Felegetibeb Sunday school EOTC

በጎ አድራጎት ክፍል

ክፍሉ በስሩ የፕሮጀክት ጥናትና ትግበራ ን/ክፍል፣ የመርሐግብር ዝግጅት፣ ቅስቀሳና ገቢ አሰባሳቢ ን/ክፍልና የበጎ አድራጊ አባላት ክትትልና ምዝገባ ን/ክፍል ሲኖሩት ተጠሪነቱ ለስራ አስፈጻሚ ሆኖ የሚከተሉትን ተግባርና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፡፡

  • በሰ/ት/ቤት አባልነት ተመዝግበው በአባላት ክትትልና ግንኙነት ክፍል ተለይቶ የቀረቡለትን እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን አባላት እንዲረዱ ያደርጋል
  • አባላትና ነዲያን በቋሚነት የሚረዱበትን ቋሚ ፕሮጀክት አዘጋጅቶ ሲጸድቅለት ተግባራዊ ያደርጋል
  • ልዩ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብሮችን ያዘጋጃል፣ ቅስቀሳ ያደርጋል
  • ነዲያን በአበይት በዓላት የአልባሳትና መስተንግዶ አገልግሎት እንዲያገኙ ያደርጋል