የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል አገልግሎት ክፍል ከላይ በአባልና አባልነት ስር በተዘረዘረው መስፈርት መሰረት አባል ከሆኑ በኋላ ከሰ/ት/ቤት አባል የማይጠበቅ ኢ-ክርስቲያናዊ ተግባር ከታየበት ከዚህ በታች በቀረበው መሰረት አርምጃ ይወሰድበታል፡፡ የሰ/ት/ቤቱን የአጭር የመካከስኛና የረዥም ጊዜ መሪ ዕቅድ የሚመሰከታቸውን የአገልግሎት ክፍሎች በማስተባበር ያዘጋጃል፤ ክንውኑንም ይከታተላል ፤ የሰ/ት/ቤቱን አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በማጠናቀር በየአራት ወር ለሥራ አስፈጻሚ ጉባዔ ያቀርባል በጽ/ቤት ጋር በመሆን ለጠቅላላ ጉባኤ በዓመት ሁለት ገዜ በጽሑፍ ያቀርባል፡፡ የሰ/ት/ቤቱን አጠቃላይ አገልግሎት የሚገስጽ ስታትስቲክሳዊ መረጃዎችን በማሰባሰብ ስሚመለከታቸው ክፍሎች ያስተላልፋል፡፡